ከጠረፍ አደጋ ተርፎ - ማረፊያ ፍለጋ

ከሊቢያ የጠረፍ አደጋ ፍልሰተኞችን ያተረፈው የመድህን መርክብ ማቆሚያ ወደብ ፍለጋ ሲዘዋወር፤ 64 ከአደጋ የተረፉ ፍልሰተኞች የመጠጥ ውሀና የምግብ እጥረት እንደገጠማቸው የመርከቡ ባለሥልጣኖች አስታወቁ።

ሲ- አይ (Sea-Eye) የተባለው የጀርመን የሰብዓዊ ደርጅት ቡድን በሊብያ ጠርፍ ከአደጋ ያተረፋቸውን 64 ፍልሰተኞች ለስድስት ቀናት ያህል ማረፍያ ወደብ ፍለጋ ሲዘዋወር በቆየው የመድህን መርክብ ውስጥ ሰንብተዋል።

ፍልሰተኞቹ የመጠጥ ውሀና የምግብ እጥረት እንደገጠማቸው የገለጹት የመርከቡ ባለሥልጣኖች እየከፋ ሄደ ያሉት ሁኔታ እንዳሳሰባቸው መናገራቸውን ዘጋብያችን ሳቢና ካስቴልፍራንኮ ከሮም ዘግባለች። (ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

Your browser doesn’t support HTML5

ከጠረፍ አደጋ ተርፎ - ማረፊያ ፍለጋ