ትረምፕ አይዋ ላይ በከፍተኛ ድምጽ ብልጫ አሸነፉ

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

ትረምፕ አይዋ ላይ በከፍተኛ ድምጽ ብልጫ አሸነፉ

ትናንት ሰኞ ምሽት የዩናይትድ ስቴትስ አይዋ ክፍለ ግዛት ሪፐብሊካኖች "አይዋ ኮከስ" ተብለው በሚታወቁት ዝግጅቶች ተሰብስበው ከሰጡት ድምጽ፣ የቀድሞው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ ከ50 በመቶ የሚበልጠውን አግኝተው ተፎካካሪዎቻቸውን በከፍተኛ ብልጫ አሸነፉ።

የአሜሪካ ድምጹ ኬን ፋራቦ ከአይዋ "ዴሞይን" ከተማ ባጠናቀረው ዘገባ፣ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከፍተኛ ቁጥር የተሳተፈበን የ2016ቱን በማነፃፀሪያነት ጠቅሶ፣ ከኮከሱ አስቀድሞ በክፍለ ግዛቷ ላይ የወረደው አደገኛ ቅዝቃዜ የዘንድሮውን የተሳታፊ ቁጥር ዝቅ ማድረጉን ዘግቧል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ፡፡