ኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ሦስት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ የሚጠጋ ቁጥር ያለው ሰው መፈናቀሉን ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት /አይኦኤም/ አስታወቀ።
ድርጅቱ ባለፉት ነኀሴና መስከረም ባካሄደው ዳሰሳ ከሁለት ሚሊየን ተኩል በላይ የቀድሞ ተፈናቃዮች ወደየቀዬአቸው መመለሳቸውን ገልጿል።
🚨New IOM Report🚨Over 3.45 million people were internally displaced across 12 regions in Ethiopia, according to @DTM_IOM, between August and September 2023.Main causes:▶️Conflict (64%)▶️Drought (17%)▶️Social tension (9%)Press note: https://t.co/IIXzkPhpcd pic.twitter.com/gmvzO2OEqF
— IOM Ethiopia (@IOMEthiopia) January 19, 2024
አሁን ተፈናቅለው ከሚገኙት 64 ከመቶዎቹ ግጭቶችና ሁከት ያባረሯቸው መሆናቸውን ስለ ሪፖርቱ ለአሜሪካ ድምፅ ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ቃል አቀባይ ኬ ቪራይ አማራ ክልል ውስጥ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት አብዛኛው የክልል አካባቢ በአዲሱ ጥናት አለመካተቱን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ተፈናቃዮቹም ተመላሾቹም አሳሳቢ ችግሮች እንዳሉባቸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባለሥልጣን እንጉዳይ መስቀሌ ለቪኦኤ ገልፀዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ፡፡