ህንድ የራስዋን የጠፈር ጣብያ የመመስረት ዕቅድ እንዳላት አስታውቃለች። የህንድ የጠፈር አገልግሎት ሊቀ መንበር ኬ ሴቫን ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ህንድ እአአ በ2030 ከ11 ዓመታት በኋላ፣ 20 ቶን የሚሆን የጠፈር ጣብያ የመመስረት ዕቅድ አላት ብለዋል።
ዋሺንግተን ዲሲ —
ህንድ የጠፈር ጣብያውን ምስረታ በሚመለከት ከማንኛዋም ሀገር ጋር አትተባበርም ሲሉም አክለዋል። የጠፈር ጣብያው የሚያስፈልገው የመጀመርያውን የህንድን የሰዎች የጠፈር በረራን ለመደገፍ ነው ብለዋል።