"የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ ህጋዊ ነው” - ሙሳ ፋኪ ማሃማት

  • እስክንድር ፍሬው

በኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ ላይ 

የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ “ህጋዊ ነው” ሲሉየአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ተናግረዋል።

“የአገሪቱን አንድነትና መረጋጋት እንደዚሁም ሕገመንግሥታዊ ስርዓቷን ለመጠበቅ የተወሰደቆራጥ እርምጃ ነው” ብለዋል ሊቀመንበሩ በኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ ላይ ዛሬ ሲናገሩ።

የኅብረቱ ሊቀመንበር ያሰሙትን ቃል “እንደ ዲፕሎማሲያዊ ድል ይቆጠራል” ያለው የኢትዮጵያ መንግሥት የአፍሪካ ህብረትም ሆነ የኢጋድ አቋም የአባል አገራቱ አቋም መሆኑን ጠቅሷል።

በሌላም በኩል የኢትዮጵያ እና የሱዳን የጋራ ድንበር ኮሚሽን ስብሰባ ሰሞኑን በሁለቱ አገሮችአዋሳኝ አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት ዙሪያ እንደሚነጋገር ተገልጿል::

Your browser doesn’t support HTML5

"የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ ህጋዊ ነው” - ሙሳ ፋኪ ማሃማት