የወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ድሬ ዳዋ ላይ በዝግ ተቀምጧል

Your browser doesn’t support HTML5

የወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ድሬ ዳዋ ላይ በዝግ ተቀምጧል

በወሰኖችና በማንነት ዙሪያ በ68 ዞኖች ላይ ባካሄደው የመጀመሪያ ጥናት ውጤት ላይ ከኅብረትሰቡ ጋር በዝግ ምክክር ማካሄድ መጀመሩን የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን አስታውቋል።

ድሬ ዳዋ ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው ህዝባዊ ውይይት ወደፊትም መገናኛ ብዙኃንን እና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያካተተ ውይይት እንደሚያካሂድ ኮሚሽኑ ጠቁሞ በአስተዳደር ወሰንና በማንነት ጉዳይ ላይ ያሉ ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል የሚለውን ሃሳብ እንደሚያቀርብ አመልክቷል።