የድርቅ ጫና እና የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ድጋፍ

Your browser doesn’t support HTML5

ላለፉት ሁለት ዓመታት ዝናብ መጥፋቱን ተከትሎ በሶማሌ ክልል ከሦስት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለምግብ እጥረት ተዳርገዋል።

የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ሙስጠፋ መሐመድ ዑመር ሰሞኑን በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴስት ኤምባሲ ጉዳይ ፈፃሚ አምባሳደር ትሪሲ ጄከብሰን በክልሉ ተቀብለው ድርቁ እያደረሰ ስላለዉ ጫና እንዲሁም እየተደረገ ስላለዉ ሰብአዊ ድጋፍ መክረዋል።

አምባሳደር ትሪሲ ጄከብሰን ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚውል ተጨማሪ ድጋፍ ማቅረቧንም በጉብኝታቸው ወቅት ይፋ አድርገዋል።