የሐረሪ ክልል ምክር ቤት የክልሉን በጀት አፀደቀ

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት የክልሉን በጀት ከ3 ወራት ገደማ መጓተት በኋላ አፀደቀ።

አዲስ የተሾሙት የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ በጀቱ ቶሎ ሊፀድቅ ያልቻለው ሃገራዊ ለውጡን በክልሉም ለመተግበር አስቀድሞ የአደረጃጀት ማሻሻያ ጥናቶች እየተጠኑ ስለነበር ነው ብለዋል።

በክልሉ የነበረው የካቢኔ ወንበርም ከ10 ወደ 14 ያደገ ሲሆን በአዲሱ የሥልጣን ክፍፍልም የሀርሪ ብሄራዊ ሊግና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እኩል ስባት፣ ስባት ወንበር ይኖራቸዋል ተብሏል።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት የክልሉን በጀት አፀደቀ