ያለ ዕድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም ያስችላሉ የተባሉ ሰነዶች ይፋ ሆኑ

  • እስክንድር ፍሬው

Your browser doesn’t support HTML5

ያለ ዕድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም ያስችላሉ የተባሉ ሰነዶች ይፋ ሆኑ

የሴት ልጅ ግርዛትና ያለ ዕድሜ ጋብቻን ለማስቆም አሁንም የተቀናጀ ስራ እንደሚያስፈልግ የገለፀው የኢትዮጵያ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒሰቴር፣ ከተባበሩት መንግሥታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመተባበር ያዘጋጃቸውን ሰነዶች ዛሬ ይፋ አድርጓል ።

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ/ም ይፋ የተደረጉት ብሔራዊ የዕቅድ ሰነዶች ችግሩን እ.አ. አ. እሰከ 2030 ለመፍታት ያስችላሉ የተባሉ ናቸው።

የተፈጥሮ አደጋዎች እና ግጭቶች ታዳጊ ሴቶችን ለተጠቀሱት ችግሮች እያጋለጡ መሆኑን የተናገሩት፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ምኒሰትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ "ትልቁ ነገር ሰላም ላይ መስራት ነው" ብለዋል።

ድርጊቶቹ ሰብዓዊ ቀውስ በሌለበት ሁኔታ ውስጥም እየተፈጸሙ ናቸው ያሉት በኢትዮጵያ የዩኒሴፍ ተጠባባቂ ተወካይ ማሪኮ ካጎሺማ፣ ሰነዶቹ የግንዛቤ ለውጥ ለማምጣት እንደሚያግዙ ጠቅሰዋል።