የዓለም ገበያ

  • ቪኦኤ ዜና

ፎቶ ፋይል

ዛሬ በዓለም ደረጃ ያለው የአክስዮን ገበያ ሁኔታ ድብልቅ ነው ተብሏል። በእስያ ያሉት የአክስዮን ገበያዎች ሲወርዱ የአውሮፓዎቹ ግን ከፍ ብለዋል።

የጃፓን ኒኬይ መለኪያ በ 2.3 ከመቶ ተዘግቷል። የሆንግ ኮንጉ ሀንግ ሴንግ በ 0.7 መለኪያ ተዘግቷል።

የኢንግላንድ ባንክ በኮሮናቫይረስ መዛመት ምክንያት የወለዱን መጠን ከአንድ ከመቶ ግማሽ በመቀነሱ የለንደኑ /FTSE/ አክስዮን ከፍ ብሏል።

የጀርመንና የፈረንሳይ ገበያዎች አክስዮኖች ዋጋ ከፍ ብሏል።

ሦስት ዋና የዩናይትድ ስቴትስ ኢንደክሶች ዳው ጆንስ፣ /S and P 500/ እና ናስዳክ ትላንት ትልቅ ገቢ አግኝተው ነበር። ሦስቱም እስከ 5 ከመቶ በማግኘት ነው የዘጉት።