ጋና የገጠማትን የኢኮኖሚ ቀውስ ለመፍታት ተመራጩ ፕሬዝደንት የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ተጠየቀ

  • ቪኦኤ ዜና

የምርጫ ቦርድ ባለሥልጣናት ድምፅ ቆጠራ ላይ እአአ ታኅሣሥ 7/2024

Your browser doesn’t support HTML5

ጋና የገጠማትን የኢኮኖሚ ቀውስ ለመፍታት ተመራጩ ፕሬዝደንት የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ተጠየቀ

የቀድሞ የጋና ፕሬዝደንት እና የተቃዋሚ መሪው ጃን ማሃማ ባለፈው ቅዳሜ በተደረገው ምርጫ ማሸነፋቸውን የሃገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ዛሬ ሰኞ አስታውቋል። ማሃማ ወደ ሥልጣን የመመለሳቸው ጉዳይ የተደበላለቁ አስተያየቶችን በማስተናገድ ላይ ነው። አንዳንዶች ማሃማት በአዲስ መልክ ለማስተዳደር በመመለሳቸው ደስታቸውን ሲገልጹ፣ ሌሎች ደግሞ የጋናን የኢኮኖሚ ተግዳሮቶች የመፍታት አቅማቸው ላይ ጥያቄ አላቸው።

የቪኦኤው ሰናኑ ቶድ ከአክራ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።