ዜና ዕረፍት

ወይዘሮ ገነት ዘውዴ

ባልደረባችን ሰሎሞን ክፍሌ ባለቤቱን አጥቷል፡፡

ወይዘሮ ገነት ዘውዴ

Your browser doesn’t support HTML5

ባልደረባችን ሰሎሞን ክፍሌ ባለቤቱን አጥቷል


የሰሎሞን ክፍሌ ባለቤት ወ/ሮ ገነት ዘውዴ ያረፈችው በጠና ታምማ ላለፉት ሦስት ወራት ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ጆርጅ ዋሽንግተን ሆስፒታል በሕክምና ስትረዳ ከቆየች በኋላ ነው፡፡

ወ/ሮ ገነት ያረፈችው በቅርብ ሲንከባከቧት በነበሩት ባለቤቷ፣ ልጅዋ እናቷ፣ አክስቷና ሌሎችም የቤተሰብ አባላትና የቤተሰቡ ወዳጆች በተገኙበት ነው፡፡

ወ/ሮ ገነት ዘውዴና አቶ ሰሎሞን ክፍሌ በረዥሙ የትዳር ዘመናቸው አንዲት ልጅ አፍርተዋል፡፡

ወይዘሮ ገነት ዘውዴ

የወ/ሮ ገነት ዘውዴ ቤተሰቦች አርሊንግተን ቨርጂንያ፤ ኮሎምቢያ ፓይክ ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አዳራሽ ውስጥ ዘመድ ወዳጅን እያስተናገዱ ሲሆን የፊታችን ሐሙስ፤ አፕሪል 3/2006 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲ.ሲ በምትገኘው ርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የፀሎት ሥነ-ሥርዓት ተከናውኖ አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሃገሯ ኢትዮጵያ በዚያው የሚሸኝ መሆኑን የቤተሰቡ አባላት ገልፀዋል፡፡

የቪኦኤ ባልደረቦች በተወዳጅዋ ጓደኛችን ወ/ሮ ገነት ዘውዴ ዕረፍት በእጅጉ አዝነናል፤ ለመላ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመድ መፅናናትን እንመኛለን፡፡