ከሊብያ ወደ ሰሜን ቻድ በሰልፍ ያመሩ የነበሩ 40 ፒክ-አፖ መኪናዋችን እንደመለሰ፣ የፈረንሳይ ወታደራዊ ጦር አስታወቀ።
ዋሺንግተን ዲሲ —
የፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስቴር በዛሬው ቀን እንዳስታወቀው፣ የተሸርካሪዎቹን ጉዞ ለመግታት /Mirage 2000/ ተዋጊ ጄቶችን ተጠቅሟል።
ጣልቃ-ገብነቱ የተካሄደው ከቻድ ባለሥልጣናት በቀረበ ጥያቄ መሠረት መሆኑን ያስታወቀው የፈረንሳይ ወታደራዊ ጦር፣ ዕርምጃውም "የጠላትነ" ያለውን አካሄድ ሊያስቀር እንደቻለም አመልክቷል።
ለዚህ ከሊብያ ለተንቀሳቀሰው የወረራ ጉዞ፣ ኃላፊነት የወሰደ ወገን አልቀረበም።