ኢህአዴግ ዶ/ር አብይን መምረጡ እንዳስደሰታቸው የቀድሞ የፓርላማ አባል ገለፁ

  • መለስካቸው አምሃ
የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ ዶ/ር አብይ አህመድን በሊቀመንበርነት በመምረጡ መደሰታቸውን አንድ የቀድሞ የፓርላማ አባል ተናገሩ፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ ዶ/ር አብይ አህመድን በሊቀመንበርነት በመምረጡ መደሰታቸውን አንድ የቀድሞ የፓርላማ አባል ተናገሩ፡፡

ዶ/ር አብይ ለፓርላማው የሚያሰሙት የሹመት ንግግራቸው ስለ ሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር መስፋትና ስለፖለቲካ እስረኞች ፍቺ ጉዳይ ማካተት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡

እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ከ2002 እስከ 2007 ዓ.ም የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ ግርማ ሰይፉ ኢህአዴግ ዶ/ር አብይ አህመድን በሊቀመንበርነት መምረጡ እንደብዙ ኢትዮጵያውያን ያስደሰታቸው መሆኑን ለቪኦኤ ገለፁ፡፡

በርሳቸው አስተያየት ኢህአዴግ ሊቀመንበሩን እንዴት መረጠ ከሚል ሰፋ ተደርጎ መታየት እንዳለበትም አቶ ግርማ ሰይፉ ያስገነዝባሉ፡፡

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ኢህአዴግ ዶ/ር አብይን መምረጡ እንዳስደሰታቸው የቀድሞ የፓርላማ አባል ገለፁ