የሐዋሳ የዓሳ ገበያ ቢነቃቃም የምርቱ መጠን በሚፈለገው መጠን አላደገም

Your browser doesn’t support HTML5

የሐዋሳ የዓሳ ገበያ ቢነቃቃም የምርቱ መጠን በሚፈለገው መጠን አላደገም

በተለይ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በተለያየ አማራጭ እየቀረበ ያለው የሐዋሳ ሀይቅ ዓሳ፣ ገበያው እንዲነቃቃ ቢያደርግም የምርቱ መጠን በሚፈለገው ደረጃ አለመሆኑን ተጠቃሚዎች እና ባለስልጣናት ተናገሩ።

ይሄም ሆኖ፣የሐዋሳ የዓሳ ገበያ ለአስጋሪዎች ለ667 ወጣቶች የሥራ እድል እንደፈጠረላቸው የከተማው ህብረት ስራ ማህበር መስሪያ ቤት አስታውቋል።

የሐዋሳ ከተማ ግብርና መምሪያ በበኩሉ ካለው አቅም በታች ቢኾንም፣ ከሐይቁ በየዓመቱ 450 ቶን የዓሳ ምርት ለገበያ እንደሚቀርብ ገልጿል።

ኢትዮጵያ ባለፈው ዐመት 131 ሺህ ቶን ዓሳ ብቻ ማምረቷን የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል።