ሁለተኛው የፍቼ ጫምባላላ ክብረ በዓል በዋሽንግተን ዲሲ

Your browser doesn’t support HTML5

ሁለተኛው የፍቼ ጫምባላላ ክብረ በዓል በዋሽንግተን ዲሲ

በዩናይትድ ስቴትስ የሚኖሩ የሲዳማ ብሔር ተወላጆች፣ በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ የፍቼ ጨምበላላን በዓል አክብረዋል።

በዓሉ፣ ጠበኞች ችግራቸውን በሰላም እና በውይይት የሚፈቱበት ዕሴት እንዳለው የገለጹ የበዓሉ ተሳታፊዎች፣ በአገራቸው የተባባሰው የሰላም ዕጦት እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል፡፡

በበዓሉ ላይ በእንግድነት የተገኙት በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ፣ መንግሥታቸው በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተከሠተውን ጦርነት በሰላም እንዲፈታ ማድረጉን ገልጸዋል፤ አሁን ያሉ ግጭቶችም በሰላም እና ውይይት እንዲፈቱ ይሠራል፤ ብለዋል፡፡