የኢዜማ መግለጫ

  • መለስካቸው አምሃ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትኅ ፓርቲ /ኢዜማ/ ባለፈው ሳምንት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ አደጋ ያደረሱ ናቸው ያላቸው ሰዎች ሁሉ ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠየቀ፡፡

በችግሩ ምክንያት ጉዳይ የደረሰባቸው ሁሉ ተገቢው ካሳ እንዲከፈላቸው እና ከቀያቸው የተፈናቀሉትም በአስቸካይ ተመልሰው እንዲቋቋሙ ጥሪ አቀረበ፡፡

ፓርቲው ዛሬ ከቀትር በኋላ በጠራው ጋዜጣዊ ጉባኤ ላይ ባሰራጨው የፁሁፍ መግለጫ የህዝብን በተለይም የወጣቱን ሁለንተናዊ ደኅንነትና የኢኮኖሚ ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስ የሚቻለው ህዝብ በነፃነት በመረጣቸውና የተሻለ ሀሳብ ያላቸው መሪዎች ሲተዳደርና እውነተኛ ፌዴራላዊ የአስተዳደር ሥርዓት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን ይገልፃል፡፡

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የኢዜማ መግለጫ