በቅርቡ ከአገር ተሰዶ የወጣው የማራኪ መጽሔት ማኔጂንግ ኤዲተር አረፈ።

Your browser doesn’t support HTML5

በቅርቡ ከአገር ተሰዶ የወጣው የማራኪ መጽሔት ማኔጂንግ ኤዲተር አረፈ።

Your browser doesn’t support HTML5

የሚሊዮን ሹሩቤን ህልፈት ተከትሎ ከሞያ ጓደኞቹ ጋር የተካሄደውን ሙሉ ቃለ ምልልስ ከዚህ ያድምጡ፤

በስደት ላይ የሚገኘው የማራኪ መጽሔት ማኔጂንግ ኤዲተር ሚልዮን ሹርቤ ባደረበት ህመም በትላንትናው እለት አረፈ።

ሚልዮን፤ “በኢትዮጵያ መንግስት ወከባ እየደረሰብን ነው፤” ባሉት ወከባ ሳቢያ በቅርቡ ከአገር ተሰደው ወደ ጎረቤት አገሮች ከኮበለሉ የመጽሔት አዘጋጆችና አሳታሚዎች አንዱ ነበር።

ሚልዮን የሕክምና እርዳታ ያገኝ ዘንድ በጓደኞቹ አማካኝነት በቀረበለት ጥያቄ መሠረት እገዛ ያደረገው ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት CPJ የምሥራቅ አፍሪቃ ቢሮ ተጠሪ Tom Rhodes በጋዜጠኝነት ሥራ በተሰማሩበት በሚገጥማቸው ወከባ ሳቢያ አገራቸውን ጥለው ለመኮበልል የሚገደዱ ጋዜጠኞች ብዙዎቹ ለተለያዩ በሽታዎችና ለባሰ እንግልት ይጋለጣሉ፤ ይላል። አንዳንዱ በቀላሉ ሊታከሙ የሚችሉ የበሽታ ዓይነቶች ቢሆኑም እንዲህ እንዳሁኑ የከፋ ውጤት የሚያስከትሉበት ጊዜ ግን ጥቂት አይደለም፤ ብሏል።