የሳውዲ አረብያን መንግስት በመቃወም በዋሽንግተን ዲሲ ኢትዮጵያውያን አደባባይ ወጡ

EthiopiansRalleySaudi.001.11.17.13.jpg

Your browser doesn’t support HTML5

የሳውዲ አረብያን መንግስት በመቃወም በዋሽንግተን ዲሲ ኢትዮጵያውያን አደባባይ ወጡ


የሳውዲ አረብያ መንግስት በቅርቡ “የመኖርያ ፈቃድ የላቸውም፤” ያላቸውን በዚያች አገር የሚኖሩ የውጭ አገር ሠራተኞች ለማስወጣት በያዘው ዘመቻ ከፍተኛ ግፍና በደል የደረሰባቸው ወገኖቻቸው ጉዳይ ነው በቁጣ ግልብጥ ያሉት ሠልፈኞች በዛሬው ዕለት ለቅዋሜ አደባባይ የወጡት።

በብዙ መቶዎች የተቆጠሩት ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን ከዋሽንግተን ዲሲው የሳውዲ ኤምባሲ ደጃፍ ባካሄዱት በዚህ ሠልፍ፥ የሳውዲ መንግስት ‘ከአገሬ ውጡ!’ ያላቸውን የተለያዩ አገር ዜጎች የሰብዓዊ መብት እንዲያከብር፥ የኃይል እርምጃውን እንዲያስቆምና ተጠያቂ ይሆን ዘንድ ከልዩ-ልዩ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች የመጡትን ጨምሮ የተለያዩ የሃይማኖት መሪዎችና የማኅበራት ተጠሪዎች ባሰሙት ጥሪ ጠይቀዋል።

የዘገባውን ዝርዝር ለመስማት የሚቀጥለውን ይጫኑ።

Your browser doesn’t support HTML5

የሳውዲ አረብያን መንግስት በመቃወም በዋሽንግተን ዲሲ ኢትዮጵያውያን አደባባይ ወጡ