የጠቅላይ ሚንስትሩ የዩናይትድ ስቴትስ ጉዞ እና ክንውን ሲገመገም

ቴዎድሮስ ፀጋዬ እና ሼክስፒር ፈይሳ

"ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት የባሕር በር ጉዳይ መጠየቅ በጦርነት ናፍቆት ይመሰላል። የተሳሳተ አተያይ።.መጀመሪያ የሕግ የተፈጥሮና የታሪክ መብት ያለን መሆኑን የሚቀበል አስተዳደር ይኑረን ነው። ከመቀበል ነው የሚጀምረው።"- ቴዎድሮስ ጸጋዬ "በሃሳቡ ብስማማም። ይሄ ጥያቄ ግን አሁን አንገብጋቢው ጥያቄ አይደለም። ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት የተፈጸሙና ብዙ መስተካከል ያለባቸው፤ ለኢትዮጵያ ሕልውናም አንገብጋቢ የሆኑ ጉዳዮች አሉ።" - ሼስፒር ፈይሳ

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አሕመድ የስድስት ቀናት የዩናይትድ ስቴትስ ቆይታ፣ ክንውንና አንድምታ የሚመረምር ውይይት ነው።

ሼክስፒር ፈይሳ በዩናይትድ ስቴትሷ የሲያትል ዋሽንግትን ከተማ በጥብቅና ሞያ የተሰማራ ትውልደ-ኢትዮጵያዊ ነው።

ቴዎድሮስ ጸጋዬ የርዕዮት ሚዲያ ሥራ አስኪያጅ እና ጋዜጠኛ ነው። በተለያዩ መድረኮች ያነሷቸውን ከጉዳዩ ጋር የተዛመዱ ጭብጦች ጨምሮ በጠቅላይ ሚንስትሩ የዩናይትድ ስቴትስ ጉዞ እና የውይይት መድረኮች ገጽታ ዙሪያ ጠበቅ አድርገው ይከራከራሉ።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

Your browser doesn’t support HTML5

የጠቅላይ ሚንስትሩ የዩናይትድ ስቴትስ ጉዞ እና ክንውን ሲገመገም

Your browser doesn’t support HTML5

የጠቅላይ ሚንስትሩ የዩናይትድ ስቴትስ ጉዞ እና ክንውን ሲገመገም