በኦባማ ንግግር የተቀየሙት የተቃዋሚ መሪዎች

제임스 코미 전 미 연방수사국(FBI) 국장이 상원 정보위 청문회에서 증인 선서를 하고있다.

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ስለ ኢትዮጵያ ምርጫ የሰጡት አስተያየት “በጎውን ንግግራቸውን ሁሉ የሻረ ነው” ሲሉ የመድረክ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ተናገሩ።

Your browser doesn’t support HTML5

በኦባማ ንግግር የተቀየሙት የተቃዋሚ መሪዎች

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ስለ ኢትዮጵያ ምርጫ የሰጡት አስተያየት “በጎውን ንግግራቸውን ሁሉ የሻረ ነው” ሲሉ የመድረክ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ተናገሩ።

ይህ አስተያየት በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ተስፋ ላይ ጉዳት ያደረሰ ነው ሲሉም አብራርተዋል።

ፕሬዘዳንት ኦባማ የኢሕአዴግ ደጋፊ በሆኑ ባለሥልጣኖቻቸው ተከብበዋል በማለትም ፕሮፌሰር በየነ አስረድተዋል።

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነትም ፕሬዘዳንት ኦባማ ስለ ኢትዮጵያ ምርጫ የሰጡትን አስተያየት ከተቃወሙ መካከል አንደኛው ናቸው፡፡

“የኦባማ ንግግር ቅር ስላሰኘኝና የፖለቲካ ተቃዋሚዎችና ጋዜጠኞች እየተዋከቡና እየታሠሩ ባለበት ባሁኑ ወቅት፤ የቤተ መንግሥቱን የራት ግብዣ መቀበል ሕሊናዬ አይፈቅድም” በማለት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት መቅረታቸው ተዘግቧል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡