በዘንድሮ የ12 ክፍል ተፈታኞች 95 በመቶ የሚጠጉት ፈተናውን ያለማለፋቸው ተነገረ

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ

Your browser doesn’t support HTML5

በዘንድሮ የ12 ክፍል ተፈታኞች 95 በመቶ የሚጠጉት ፈተናውን ያለማለፋቸው ተነገረ

እየተገባደደ ባለው 2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱት ከ674 ሺህ በላይ ተፈታኞች፣ ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ማለፊያ ውጤት ያመጡት 5.4 በመቶ ወይም 36 ሺህ 409 ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።

ይህ ውጤት ካለፈው አመት የተሻለ መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሩ፣ በአመቱ ተማሪዎችን ካስፈተኑት ት/ቤቶች ውስጥ 1 ሺህ 363 የሚሆኑ አንድም ተማሪ እንዳላሳለፉ ተናግረዋል፡፡