የየመንዋ ወደብ ከተማ ሁዴይዳ እና ኢትዮጵያውያን ስደተኞች

Your browser doesn’t support HTML5

የተባበሩት መንግስታት የደህንነት ምክር ቤት በየመን የሁዴዳን ከተማን ፀጥታ በተመለከተ ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠዋል። በሳዑዲ አረቢያ የሚመራው የአረብ አገሮች ጣምራ ጦር በሁቲ አማፅያን ቁጥጥር ስር በሆነችው የየመን ዋና የባህር በር ሁዴዳ ላይ ጥቃት በማድረስ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታትና ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩት የከተማዋ ነዋሪዎችና በሃገሪቱ በሚልየን የሚቆጠሩት ዜጎች ለረሃብና ለተለያዩ በሽታዎች እንድሚጋለጡ ተናገሩ።