ዶ/ር ቴድሮስ የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርነት እንዲመረጡ አፍሪካዊያን ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል

  • እስክንድር ፍሬው

የቀድሞ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ማርጋሪት ቻን እና የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተመረጡት ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም

ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ሆነው እንዲመረጡ አፍሪካዊያን የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ሆነው እንዲመረጡ አፍሪካዊያን የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አቶ መለስ ዓለም እንዳሉት ምርጫው ዶ/ር ቴድሮስና ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ ላስመዘገቡት ውጤት የተሰጠ ዕውቅና ነው፡፡

ምርጫው አንድ አፍሪካ አንድ ድምፅ የሚለው አቋም ተግባራዊ መደረጉ የታየበት ነው ያሉት ደግሞ የፓን አፍሪካ ፓርላማ የክብር ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊወርጊስ ናቸው፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ዶ/ር ቴድሮስ የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርነት እንዲመረጡ አፍሪካዊያን ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል