የአገር ጉዳይ:- በኢትዮጵያ የሚታየው የፖለቲካ ቀውስ ያስከተለው ውጥረትና መጪው ጊዜ

Ethiopia Political Crisis

“የአገር ጉዳይ” በሚል ርዕስ በራዲዮ መጽሔት እየተሰናዳ በሚቀርበው ልዩ ተከታታይ ፕሮግራም የተጀመረ ውይይት ነው።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ የሚጻፉ፥ የሚታዩና የሚሰሙ ዜናዎችና ዘገባዎች የሚቀርቡባቸው የአራት መደበኛና የአካባቢ መገናኛ ብዙኃን መድረኮች አዘጋጆችና ባለቤቶች ናቸው።

የኢትዮ-ሚድያው ዋና አዘጋጅ አብረሃ በላይ፤ የኢሳት ራዲዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራሞች አዘጋጅና አቅራቢው ሲሳይ አጌና፥ የአዲስ አበባው Horn affairs የተሰኘ የኦንላይን መጽሔት አዘጋጅ ዳንኤል ብርሃኔ እና እንዲሁም በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ፤ በኢንተርኔትና በስልክ በሌሎች አካባቢዎችም ጭምር የሚሰማው “አዲስ ድምጽ” የተባለው የማሕበረሰብ ራዲዮ አዘጋጅና አቅራቢ አበበ በለው ናቸው።

የፖለቲካ ቀውስና በኃይል የታጀቡ እንቅስቃሴዎች እንደምን ባለ ላፊነት ይዘገባሉ? ... አሳሳቢ ሁኔታዎች በሚታዩበት የዛሬዋ ኢትዮጵያስ የመገናኛ ብዙኃን ሚናና ኃላፊነት ምንድ ነው?

ተከታታይ ውይይቶቹን ከዚህ ያድምጡ

Your browser doesn’t support HTML5

የአገር ጉዳይ:- የኢትዮጵያ የሚታየው የፖለቲካ ቀውስና ውጥረት .. (ክፍል አንድ)

Your browser doesn’t support HTML5

የአገር ጉዳይ:- የኢትዮጵያ የሚታየው የፖለቲካ ቀውስና ውጥረት .. (ክፍል ሁለት)