አሁንም ህይወት እየቀጠፈ ያለው የትራፊክ አደጋ

ፎቶ ፋይል፦ አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

ፎቶ ፋይል፦ አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ በሚደርሱ የትራፊክ አደጋዎች ዋነኛ ተጎጅዎቹ ወጣቶች መኾናቸው የሚደርሰውን ሰብአዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ከፍ እንዲል አድርጎታል ሲሉ ባለሞያዎች ይናገራሉ፡፡

ለችግሩ ዘላቂ መፍተሔ ለማምጣትም መንግሥት በትኩረት እንዲሠራ አሳስበዋል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

አሁንም ህይወት እየቀጠፈ ያለው የትራፊክ አደጋ

የኢትዮጵያ መንገድ ደኅንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት በበኩሉ የትራፊክ አደጋ አሁንም ሀገራዊ ስጋት መሆኑን ጠቅሶ የተጎጅዎች መጠን ግን እየቀነሰ መምጣቱን አስታውቋል፡፡

የመንገድ ደኅንነትነትን በትምህርት ስርዐት ውስጥ እንዲካተትና የሕግ ማሻሽያዎችን በማድረግ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት እየሠራሁ ነው ብሏል፡፡ ዝርዝር ዘገባው ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።