በሁከትና ብጥብጥ ተጠርጥረው ከኦሮሚያ ከድቡንና ከአማራ ክልሎች የተያዙና የተሃድሶ ስልጠና ወስዱ የተባሉ ከ11ሺሕ በላይ እስረኞች መለቀቃቸውን የመንግሥት መገናኛ ገልፀዋል፡፡
አዲስ አበባ —
በትናንትናው ዕለት መለቀቃቸው እና ከቤተሠቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸው የተዘገበው በሁለተኛ ዙር በተለያዩ ቦታዎች የተሃድሶ ሥልጠና የወሰዱ ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በሰንቀሌ ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ የተሃድሶ ሥልጠና የወሱዱ ከ3ሺሕ 8መቶ ሠልጣኞች ወደ የመጡበት መመለሳቸው በመንግሥት የመገናኛ ብዙሃን ተዘግቧል፡፡
እስክንድር ፍሬው ዘገባውን አድርሶናል፡፡ ቆንጂት ታዮ የተቃዋሚ መሪዎች ታሣሪዎቹን መለቀቅ ላይ የሰጡትን መልስ ይዛለች አያይዘን እናቀርባለን፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
መንግሥት ከ11ሺሕ በላይ ታራሚዎችን ፈታ