“ከምንዛሬ ለውጥ በኋላ የምግብ ዋጋ የተፈራውን ያህል አልጨመረም” የኢትዮጵያ የዋጋ ሪፖርት

መርካቶ ገበያ፣ አዲስ አበባ

Your browser doesn’t support HTML5

“ከምንዛሬ ለውጥ በኋላ የምግብ ዋጋ የተፈራውን ያህል አልጨመረም” የኢትዮጵያ የዋጋ ሪፖርት

ኢትዮጵያ በአብዛኛው በአገር ውስጥ ምርት ላይ ጥገኛ በመሆኗ እና በሌሎች ምክንያቶች የምግብ ዋጋ አስቀድሞ የተፈራውን ያህል ያለመጨመሩን የጠቀሰው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሪፖርት አመለከተ።

የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ትላንት የጠቀሰው ሪፖርት፣ ከውጭ በሚገቡ የፍጆታ እቃዎች ላይ ግን ከፍ ያለ ጭማሪ መታየቱን አመልክቷል፡፡

እስካሁን የምግብ ዋጋ ጭማሪዎች ቢኖሩትም የተጠበቀውን ያህል ጭማሪ ሳይታይበት ለመቀጠሉ የተለያዩ ምክንያቶችን የሚያስቀምጡት የምጣኔ ኃብት ባለሙያዎችበበኩላቸው፣ በቀጣይነት ግን ከመደበኛው በተለየ ከፍ ያለ ጭማሪ የሚያስከትሉ ሁኔታዎችና እርምጃዎች መኖራቸውን ያስረዳሉ፡፡