የፖስፖርት የግዜ ገደብ ወደ 10 ዓመት ሊራዘም ነው

ኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት

ኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት

Your browser doesn’t support HTML5

የፖስፖርት የግዜ ገደብ ወደ 10 ዓመት ሊራዘም ነው

በኢትዮጵያ የሚሰጠው ፖስፖርት፣ የአገልግሎት ቆይታው ከ5 ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ እንደሚል፣ የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ከአንድ ወር በኋላ በሚጀመረው አዲስ አሠራር መሰረት የሚሰጠው ፖስፖርት ለ 10 ዓመት የሚያገለግል ይሆናል ብለዋል፡፡

መሥሪያ ቤቱ፣ በዚህ ዓመት የቤት ለቤት የፓስፖርት ማደል አገልግሎት እንደሚጀምርም ዋና ዲሬክተሯ ተናግረዋል፡፡