“ማንኛውም መሪ ወጣትን መምራት ካልቻለ ሕዝብን እመራለሁ ማለት አይችልም” - ከሰልፈኞቹ አንዱ

በዱከም ከተማ የ "eastern industrial zone’ ሠራተኞች ያደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞችና ወረዳዎች ውስጥ “ግድያ ይቁም” የሚል መልዕክት ያነገቡ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ እያካሂዱ መሆኑን ገለፁ። በተለያየ ከተማ የሚገኙ ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምጽ እንደተናገሩት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየጠፋ ያለው የሰው ሕይወት እንደዲቆም የሚጠይቅ ሰልፍ እየተካሄደ ነው ብለዋል።

በዱከም ከተማ የምስራቅ ኢንዱስትሪ መንደር ሠራተኞች በኦሮሚያ ክልል የሚደረገው ግድያ እንዲቆም የሚጠይቅ ሰልፍ ማካሄዳቸውን ተናግረዋል። ከሰለፈኞቹ አንዱም፤ “በሰልፉ ላይ የተሳተፍነው ሁላችንም ኢትዮጵያውያን በሙሉ ነን። ይቺ ሀገር የወጣት ናት። ማንኛውም መሪ ወጣትን ካልመራ ሕዝብን እመራለሁ ማለት አይችልም።” ብሏል።

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

“ማንኛውም መሪ ወጣትን መምራት ካልቻለ ሕዝብን እመራለሁ ማለት አይችልም” - ከሰልፈኞቹ አንዱ