ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ በኋላ አስራ ስድሥት አባላቶቹ መታሰራችውን መኢአድ ገለፀ

  • መለስካቸው አምሃ

የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት/መኢአድ/ ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅን ተከትሎ የታሠሩ አባላቱን እንዲፈቱ ለጠቅላይ እዙ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ቁጥራቸው አስራ አንድ ሺሕ የሚደርሱ ሰዎች ከዐዋጅ በኋላ መያዛቸውን ጠቅላይ እዙ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት/መኢአድ/ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አበበ ለቪኦኤ እንዳስታወቁት ከአስራ ስድስት የማያንሱ በፓርቲው የተለያዩ ኃላፊነት ሥፍራዎች የሚያገለግሉ አባሎች፤ ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መታወጅ በኋላ በፀጥታ ሃይሎች ቁጥጥር ሥር እንደዋሉ ተናግረዋል፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ በኋላ አስራ ስድሥት አባላቶቹ መታሰራችውን መኢአድ ገለፀ