ዲሞክራሲ በተግባር!

  • ሰሎሞን ክፍሌ
ወቅታዊው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሲገመገም።

Your browser doesn’t support HTML5

ዲሞክራሲ በተግባር!

በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት የ ‘Tom Lantos ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን’ በቅርቡ፥ ”በሁለትአስቸጋሪ ምርጫዎች መካከል አጣብቂኝ ውስጥ ያለውየወቅቱ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ” በሚል ርእስመድረክ አዘጋጅቶ የምስክሮችን ቃል አዳምጧል።

መድረኩ ባጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚታዩ የሰብአዊ መብቶችጥሰቶችን የተመለከተ ሲሆን በተለይ ግን መንግስቱ እንዴትየሲቪሉን ማህበረሰብ እንቅስቃሴ ውሱን እንዳደረገ፥ሚዲያውን እንዳፈነና በልማት ፕሮዤዎች ስም ለዘመናትባካባቢው የኖሩ ዜጎችን እንደሚያፈናቅል ፈትሿል።

በእለቱ ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጋበዙ ሰዎች፥ ዩናይትድስቴትስ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን መልካም ግንኙነትበመጠቀም፥ የሀገሪቱን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በማሻሻሉረገድ የምትረዳባቸው መንገዶች ካሉም ተወያይተዋል።