ዲስኮርስ "የሃሣብ ልውውጥ" የተሰኘ መጽሔት ተመረቀ

  • እስክንድር ፍሬው

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ

በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች የአፍሪካ ሃገሮች የውጭ ፖሊሲዎችና ምንነታቸውን በማሣወቅ ላይ ክፍተት መኖሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ አስታውቀዋል።

ሰሞኑን ይፋ የተደረገው ዲስኮርስ "የሃሣብ ልውውጥ" የተሰኘ መፅሔት ይህንን ክፍተት ለመሙላት አስተዋፅዖ እንደሚኖረው አስረድተዋል።

በእንግሊዝኛው ዲስኮርስ በአማረኛ ደግሞ "የሃሰብ ልውውጥ፣ ፍጭት ወይንም ክርክር" ተብሎ ሊጠራ የሚችለው መጽሔት በኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድም ሆነ በሃገሪቱ የመጀመሪያው እንደሆነ በምረቃው ሥነ ስርዓት ላይ ተገልጿል፡፡

መቀመጫውን አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ያደረገው የዚህ መጽሔት የመጀመሪያ ዕትም ደግሞ በተለይ የአፍሪካ ቀንድን የተመለከቱ ጹሑፎችን ይዞ ወጥቷል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ዲስኮርስ "የሃሣብ ልውውጥ" የተሰኘ መጽሔት ተመረቀ