ኢትዮጵያና ኤርትራ በመካከላቸው የነበረው የውጥረት ጦርነት መቆሙን አስታወቁ

ethio-eritrea

ኢትዮጵያና ኤርትራ በመካከላቸው የነበረው የውጥረት ጦርነት በይፋ ለማስቆም ስምምነት መፈረሙን አስታወቁ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ልዩ ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ ስምምነቱን ያብራሩልናል። በተያያዘም የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣን ከጨበጡ አንድ መቶ ቀናት ሊደፍኑ ጥቂት ቀናት የቀራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ዛሬም በአርባ ምንጭ የድጋፍ ሰልፍ ተደርጎላቸዋል።

በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የነበረውን የውጥረት ጦርነት በይፋ ለማስቆም ስምምነት መፈረሙን ሁለቱ ሀገራት አስታወቀዋልአስታወቁ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ልዩ ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ፤ ሁለቱ ሀገራት በፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ፣ በፀጥታና በደህንነት ጉዳዮች በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ያካተ ስምምነት መፈረሙን ለአሜሪካ ድምፅ አብራርተዋል።

በሌላ በኩል የኤርትራው ማስታወቅያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አስመራ ከተማ ውስጥ ስምምነቱን ሲፈርሙ የሚያሳዩ ምስሎች በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።

በሁለቱም ሀገሮች መካከል የነበረው “ጦርነት አብቅቶ አዲስ የሰላምና የወዳጅነት ዘመን ተጀምሯል ሲሉም ጽፈዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያና ኤርትራ በመካከላቸው የነበረውን የውጥረት ጦርነት መቆሙን አስታውቁ