የኢትዮጵያ ምርጫ በጊዜው እንዲካሄድ ኢሕአዴግ አቋም ይዟል

  • እስክንድር ፍሬው

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ

የፊታችን 2012 ዓ.ም መገባደጃ ላይ እንደሚካሄድ የሚጠበቀው የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ በሕገመንግሥቱ በተቀረፀው ማዕቀፍና ጊዜ እንዲካሄድ የገዥው ኢሕአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አቋም መያዙ ተገልጿል።

የተለየ አቋም የያዙ አካላት በድምፅ ካሸነፉ ግን “የምርጫው ጊዜ ይራዘም” ለሚለው ሃሣብ ለመገዛት ኢሕአዴግ ዝግጁ መሆኑን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው አባልና የግንባሩ ምክር ቤት ፅሕፈት ቤት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማኅበራት ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

የኢሕአዴግ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት አካሂዶ ባለፈው ዓርብ ምሽት ያጠናቀቀውን ስብሰባውን ውጤት አስመልክቶ አቶ ፍቃዱ ተሰማን አነጋግረናል።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ ምርጫ በጊዜው እንዲካሄድ ኢሕአዴግ አቋም ይዟል