በአዲስ አበባው የመስቀል አደባባይ የቦምብ ጥቃት ሕይወታቸው ያለፈው ሁለት ሰዎች ማንነት ይፋ ተደርጓል።
አዲስ አበባ —
በአዲስ አበባው የመስቀል አደባባይ የቦምብ ጥቃት ሕይወታቸው ያለፈው ሁለት ሰዎች ማንነት ይፋ ተደርጓል።
በጥቃቱ የተገደሉት የወላይታ ሶዶው ዮሴፍ አያሌው እና የወለጋው ቡሳ ጋዲሳ መሆናቸው ታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የሟቾቹን ቤተሰቦች ስልክ ደውለው አፅናንተዋል።
የአዲስ አበባ አስተዳደር ተጎጂዎቹንና ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃግብር መዘርጋቱን አስታውቋል።
ፍንዳታው በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ቁጣን መቀስቀሱ የተሰማ ሲሆን ሕዝቡም በያለበት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያለውን ድጋፍ መግለፁን ቀጥሏል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
በቦምብ ጥቃት ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች ማንነት ይፋ ተደርጓል