ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ቦምብ ፈነዳ

  • እስክንድር ፍሬው

ethiopia map

በአዲስ አበባ ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ትላንት ምሽት ፍንዳታ መድረሱን የዓይን እማኞች ለአሜሪካ ድምጽ ገልጸዋል።

በአዲስ አበባ ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ትላንት ምሽት ፍንዳታ መድረሱን የዓይን እማኞች ለአሜሪካ ድምጽ ገልጸዋል።

ይህንኑ ያረጋገጠው የከተማዋ ፖሊስ ኮሚሽን ማብራሪያ አልሰጠም።

ትላንት ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ከዓለም ካፌ ፊት ለፊት የደረሰው ይህ ፍንዳታ ለጊዜው ከፍተኛ መደናገጥ ፈጥሮ እንደነበር እነዚሁ ያይን እማኞች አስረድተዋል።

ፍንዳታውንና የፈጠረውን መደናገጥ ባይናቸው ከተመለከቱት መካከል የተቃዋሚው የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ የወጣቶች ሊግ አመራር አባል አቶ አዲሱ ቡላላ አንዱ ነው።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ቦምብ ፈነዳ