ኢትዮጵያ 200 በሚሆኑ አትሌቶች ላይ ህገ-ወጥ አበራታች መድሀኒት ተጥቅመው እንደሆነ ምርመራ ትጀምራለች።
ምርምራውን ካላካሄደች ያለው አማራጭ የአለም የህገ-ወጥ አበራታች መድሀኒት የሚቆጣጠረው ድርጅት (World Anti-Doping Agency)እርምጃ እንደሚገጥማት ምናልባትም ከአለም-አቀፍ የአትሌቲክስ ፌደረሽን ማህበር እገዳ ሊከተልባት እንደሚችል ተገልጿል።
ከቀኝ ወደ ግራ - የኢትዮጵያ አትለቲክስ ወኪል ሲለሺ ሽኔ፣ የኢትዮጵያ አትለቲክስ ፈደሬሽን ሃላፊ አለባቸው ንጉሴ፣ የብሄራዊ ትራክ ብድን ዶ/ር አያሌው ጥላሁን፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ህገ-ወጥ አበራታች መድሀኒት ጽ/ቤት መንግስቱ አበበ፣ ዛሬ በአዲስ አበባ ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ /ፎቶ - አሶሽየትድ ፕረስ/ሙሉጌታ አየነ/
የህገ-ወጥ አበራታች መድሀኒትን በመመርመር ረገድ አይኤኤኤፍ (IAAF) “ወሳኝ ደረጃ ላይ” ካስቀመጣቸው አምስት ሀገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ናት ተብሏል። ሌሎቹ ኬንያ፣ ሞሮኮ፣ ዩክሬይንና ቤላሩስ ናቸው።
ኬንያ የተቀመጡላትን ሁለት የጊዜ ገደቦች ባለማጠናቀቋ የህገ-ወጥ አበራታች መድሀኒት ፍተሻ ስርአትዋን ለማስተካከል እ.አ.አ. እስከ ግንቦት አስራ ሁለት ቀን ጊዜ ተስጥቷታል።
ሩስያ የህገ-ወጥ አበራታች መድሀኒትን የመቆጣጠር ስርአትዋ ችግር አለበት ተብሎ ከአለም አቀፍ የጥሎ ማለፍ ሩጫ ታግዳለች።
Your browser doesn’t support HTML5
ኢትዮጵያ 200 በሚሆኑ አትሌቶች ላይ ህገ-ወጥ አበራታች መድሀኒት ተጥቅመው እንደሆነ ምርመራ ትጀምራለች