የኢትዮጵያና የኤርትራ ድንበር ገበያተኞች

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያና የኤርትራ ድንበር ገበያተኞች

በኢትዮጵያና በኤርትራ የሰላም ስምምነት ከተደረገ በኋላ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው ድንበር ፈርሶ የእርስ በእርስ ግብይት ተጀምሯል።

የትግራይና አዲስ አበባ ታርጋ ያላቸው መካከለኛና ትላልቅ የጭነት ተሽከረካሪዎች ጤፍ፣ ሲሚንቶና ሌሎች የተለያዩ ነገሮችን ጭነው ጎዳይፍ በመባል የሚጠራው በአስመራ ደቡባዊ መውጫ በር በኩል በማራገፍ ግብይት ላይ ናቸው ተብሏል።

የተለያዩ ተሽከርካሪዎች ከአስመራ ወደ ትግራይ፣ከትግራይ ደግሞ ወደ አስመራ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ከቀን ወደቀን ኣየጨመረ በመምጣት ላይ እንደሚገኝ ወደ ሥፍራው ያቀኑት ሪፖርተሮቻችን ዘግበዋል።

(አለም ፍሰሃ ከመቀሌ ብርሃነ ብርኸ ደግሞ ከአስመራ ወደ ድንበር ተጠግተው ያሰናዱንት ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ)

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያና የኤርትራ ድንበር ገበያተኞች