ዛሬ ጠዋት ተፈጥሮ የነበረው የበርካታ በረራዎች መስተጓጎል ችግር እልባት ማግኘቱንና የተለመደው ሥራ መቀጠሉን የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡
አዲስ አበባ —
ዛሬ ጠዋት ተፈጥሮ የነበረው የበርካታ በረራዎች መስተጓጎል ችግር እልባት ማግኘቱንና የተለመደው ሥራ መቀጠሉን የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡ ችግሩ የተፈጠረው በህመም ምክንያት የቀሩ ባልደረቦቻቸው ቦታ ጭምር ሸፍነው እንዲሰሩ የተጠየቁ ሁለት የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ትዕዛዝ ባለመቀበላቸው ነው ብሏል - የኢትዮጵያ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ማኅበር እስከአሁን በጉዳዩ ላይ መግለጫ አልሰጠም ሊቀመንበሩን ለማግኘት እያደረግን የነበረው ጥረትም አልተሳካም፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5