በመንግሥት የደኅንነት ኃይሎች ተጠልፈው የተወሰዱና የደረሱበት ሳይታወቅ የቀየ ዜጎች ጉዳይ

  • እስክንድር ፍሬው

Your browser doesn’t support HTML5

በአለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት በመንግሥት የደኅንነት ኃይሎች ተጠልፈው የተወሰዱና የደረሱበት ሳይታወቅ የቀየ የዜጎች ጉዳይ መፍትኄ እንዲሰጠው ቤተሰቦቻቸው እየጠየቁ ነው፡፡

በአለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት በመንግሥት የደኅንነት ኃይሎች ተጠልፈው የተወሰዱና የደረሱበት ሳይታወቅ የቀየ የዜጎች ጉዳይ መፍትኄ እንዲሰጠው ቤተሰቦቻቸው እየጠየቁ ነው፡፡ የቤታቸው አራት ወንዶች ልጆች በሙሉ የዛሬ ሃያ አራት ዓመት በደኅንነቶች መወሰዳቸውን የገለፀች ወጣት ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ ጣልቃ እንዲገቡ ተማፅናለች፡፡

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በሰጠው ምላሽ በግል እና በቡድን የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የማየት መብት ቢኖረንም እንደዚህ ዓይነት ጥያቄዎች እስኳሁን አልቀረቡልንም ብለዋል፡፡ በደኅንነት ኃይሎች የተወሰዱና ደብዛቸው የጠፋ ሰዎች በድብቅ እስር ቤቶች ውስጥ ሊኖሩ እንደሚችሉ ይገለፁ አንድ የሕግ ባለሞያ በበኩላቸው፣ መንግሥት ይሄንን የማጣራት ግዴታ አለበት ብለዋል፡፡