አቶ ታከለ ኡማ /ኢንጂነር/ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ሆኑ

  • ቪኦኤ ዜና

የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባው አቶ ታከለ ኡማን የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባው አቶ ታከለ ኡማን የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።

የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል ባለመሆናቸው በምክትል ከንቲባነት የተሰየሙት አቶ ታከለ ኡማ የከንቲባውን ሥራ እንደሚያከናውኑ ታውቋል።

የአዲስ አበባ ከንቲባ የነበሩት አቶ ድሪባ ኩማ የአገልግሎት ዘመናቸውን ማጠናቀቃጠቸው ተገልጿል።