ኢትዮ-ቴሌኮም በዐማራ ክልል የተቋረጠውን ኢንተርኔት ለማስቀጠል “እየሠራ ነው”

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ

በዐማራ ክልል ግጭት መቀሰቀሱን ተከትሎ፣ በክልሉ የተቋረጠውን የኢንተርኔት አገልግሎት ዳግም ለማስጀመር፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋራ እየተነጋገረ መኾኑን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮ-ቴሌኮም በዐማራ ክልል የተቋረጠውን ኢንተርኔት ለማስቀጠል “እየሠራ ነው”

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬ ሕይወት ታምሩ፣ ዛሬ ረቡዕ፣ የ2016 ዓ.ም. የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሲያቀርቡ በሰጡት ማብራሪያ፣ “በክልሉ የኢንተርኔት አገልግሎት በመቋረጡ ደንበኞች ለሚያነሡት ቅሬታ ትኩረት እንሰጣለን፤” ብለዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ፥ ከውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ ከግጭት እና ከኤሌክትሪክ ኀይል መቆራረጥ ጋራ የተያያዙ ችግሮች ተቋሙን ቢፈትኑትም፣ የገቢ ዕቅዱን ግን ማሳካት መቻሉን፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።