መንግሥት አምባሳደር ማሲንጋ ባነሧቸው ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር ዝግጁነቱን ገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

መንግሥት አምባሳደር ማሲንጋ ባነሧቸው ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር ዝግጁነቱን ገለጸ

በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ፣ በሰሞኑ የፖሊሲ ንግግራቸው ባነሧቸው ጉዳዮች ላይ ለመወያየት መንግሥት ዝግጁ እንደኾነ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ፣ ዛሬ ኀሙስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያ፣ በተለያዩ የአገሪቱ ጉዳዮች ላይ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋራ መሥመሩን በጠበቀ መልኩ ለመነጋገር ያላትን ዝግጁነት ገልጸዋል፤ የአምባሳደሩን መግለጫ የተቃወመችበትን ምክንያትም አብራርተዋል።

አብዛኛዎቹን የአገሪቱን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያካተቱ ሁለት ስብስቦች በበኩላቸው፣ መንግሥት የሰጠውን ምላሽ በመተቸት፣ የአሜሪካውን አምባሳደር ንግግር እና ጥሪ እንደሚደግፉ ገልጸዋል።