የኤርትራ ልዑካን ከኢትዮጵያ ስለቀረበው የሰላም ጥሪ ለመነጋገር በያዝነው ሳምንት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ኢትዮጵያ አስታውቃለች።
ዋሺንግተን ዲሲ —
የኤርትራ ልዑካን ከኢትዮጵያ ስለቀረበው የሰላም ጥሪ ለመነጋገር በያዝነው ሳምንት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ኢትዮጵያ አስታውቃለች። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ስላስታወቀው ዜና ዝርዝር አልታናገረም።
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ባለፈው ሳምንት በሀገራቸው የሰማዕታት መታሰቢየ ዕለት ባደረጉት ንግግር መልዕክተኞች እንደሚልኩ ቃል ገብተው ነበር።