ኢህአዴግና ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ድርድሩ ከተሳታፊዎች በሚመረጥ ቋሚ ቡድን እንዲመራ ተስማሙ

  • እስክንድር ፍሬው

ኢሕአዴግና ሀገር አቀፍ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ቅድመ ድርድር

ዛሬ ለስምንተኛ ዙር የተገናኙት ኢህአዴግና ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ድርድሩ ከተሳታፊዎች በሚመረጥ ቋሚ ቡድን እንዲመራ ከስምምነት ደረሱ፡፡

ዛሬ ለስምንተኛ ዙር የተገናኙት ኢህአዴግና ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ድርድሩ ከተሳታፊዎች በሚመረጥ ቋሚ ቡድን እንዲመራ ከስምምነት ደረሱ፡፡ ድርድሩ ከፓርቲዎች ውጭ በሆነ ገለልተኛ አደራዳሪ እንዲመራ አጥብቀው ከጠየቁ ስድስቱ ፓርቲዎች አምስቱ ልዩነታቸውን እንደያዙ ሀሳባቸውን በማሻሻላቸው ነው ከስምምነት የተደረሰው፡፡

ይሕ በመሆኑም በአለፈው ሣምንታት ሲያጨቃጭቅ የቆየው ዋነኛ ርዕስ መቋጫ አግኝቷል፡፡

ገዥው ፓርቲ እና ሀገር አቀፍ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የዛሬውን የቅድመ ድርድር ውይይት የጀመሩት ከአስራ አንድ ቀን በፊት ካቆሙበት ጉዳይ በመነሳት ነው፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ኢህአዴግና ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ድርድሩ ከተሳታፊዎች በሚመረጥ ቋሚ ቡድን እንዲመራ ተስማሙ