ደቡብ አፍሪካውያን ወደ ትምህርት ቤት ለመድረስ ከሁለት ሰዓት በላይ በእግር ይጓዛሉ

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

ደቡብ አፍሪካውያን ወደ ትምህርት ቤት ለመድረስ ከሁለት ሰዓት በላይ በእግር ይጓዛሉ

በአፍሪካ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሕፃናት ተማሪዎች፣ ወደ ትምህርት ቤት ለመድረስ፣ ከአካባቢያቸው ርቀው ረጅም መንገድ በመጓዛቸው፣ ለልዩ ልዩ አካላዊ እና ሥነ ልቡናዊ ችግሮች ይጋለጣሉ፡፡ በተጨማሪም፣ በትምህርታቸው ላይም ከፍተኛ ተጽእኖ ያሳድርባቸዋል።

ለምሳሌ፡- በደቡብ አፍሪካ አንድ ግዛት ውስጥ የሚኖሩ ተማሪዎች፣ በትምህርት ገበታቸው ላይ ለመገኘት፣ ከሁለት ሰዓት በላይ በእግራቸው መጓዝ ይኖርባቸዋል።

ይህም አድካሚ ኹኔታ፣ በተማሪዎች ደኅንነት እና የትምህርት ሥርዐቱ ላይ ያደረሰውን ጫና አስመልክቶ፣ አሶሺዬትድ ፕሬስ ያጠናከረው ዘገባ፣ ነው፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።