ኡጋንድ ውስጥ አንድ ልጅ በኢቦላ በሽታ መሞቱ ታውቋል። በኡጋንዳ ጎረቤት ሀገር ኮንጎ ከአንድ ዓመት በፊት ኢቦላ የገባ ሲሆን የድንበር ዘለል ጉዳይ እንደሆነ ተመልክቷል።
የአምስት ዓመት ዕድሜው ህፃን ዛሬ እንደሞተ የሀገሪቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ያስታወቀው ኡጋንዳ ያለው የዓለም የጤና ድርጅት ጽህፈት ቤት ነው።
"The young patient - 5- year-old index case of #Ebola died last night. Two more samples were sent to UVRI and have tested positive. We, therefore, have three confirmed cases of #Ebola in #Uganda"- @JaneRuth_Aceng https://t.co/oypAqpNZEW
— WHO Uganda (@WHOUganda) June 12, 2019
ህፃኑና በርካታ የቤተሰቡ አባላት ባለፈው ሰኞ ከጎንጎ ዲሞክራቲክ ሪፖብሊክ ወደ ኡጋንዳ ከገቡ በኋላ የታመመው ልጅ በምዕርብ ኡጋንዳ ወደ ሚገኘው ካጋንዶ ሆስፒታል ተወስዶ እንደነበር የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ጄን ሩት አሴንግ ገልፀዋል።
ሚኒስትሯ አያይዘውም በሀገሪቱ ሦስት የኢቦላ በሽተኞች እንዳሉ አረጋግጠዋል። በሽታው ወደ ሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች እንዳይዛመት ዜጎች ከጤና ባለሥልጣኖች ጋር እንዲተባበሩ ባለሥልጣንዋ ጥሪ አድርገዋል።