በኪረሙ ወረዳ ጥቃት ሰባት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

Your browser doesn’t support HTML5

በኪረሙ ወረዳ ጥቃት ሰባት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በምሥራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ፣ በሁለት ቀበሌዎች ውስጥ ተፈጸመ በተባለ ጥቃት ሰባት ሰዎች መገደላቸውን፣ ነዋሪዎች እና የወረዳው ባለሥልጣናት ተናገሩ፡፡

ነዋሪዎቹ ለግድያው፣ በአካባቢው ይንቀሳቀሳሉ ያሏቸውን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊትንና የዐማራ ፋኖ ታጣቂን ሲከሱ፣ ግድያውን ያረጋገጠው የወረዳው አስተዳደር በበኩሉ፣ በጉዳዩ ላይ ክትትል እየተደረገ እንደኾነ ገልጿል፡፡