Your browser doesn’t support HTML5
የካመላ ሄሪስ የምርጫ ዘመቻ ከፍተኛ የተባለ ገንዘብ ሰበሰበ
የሪፐብሊካን ፓርቲውን ወክለው በምክትል ፕሬዝደንትነት የሚወዳደሩት ጄዲ ቫንስ፣ እርሳቸውና ዶናልድ ትረምፕ ምርጫውን አሸንፈው ዋይት ሃውስን የሚቆጣጠሩ ከሆነ፣ በፌዴራል ደረጃ በመላ ሃገሪቱ ውርጃን እንደማይከለክሉ ትላንት እሁድ አስታውቀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የዲሞክራቲክ ፓርቲውን በመወከል የሚወዳደሩት ካመላ ሄሪስ እና ቲም ዎልዝ፣ የስነ ተዋልዶ መብትን በተመለከተ ያላቸውን መልዕክት በስፋት እንዲዳረስ በማድረግ ላይ ሲሆኑ፣ የምርጫ ዘመቻቸው ደግሞ ከዚህ በፊት ያልተመዘገበ የገንዘብ መጠን ማሰባሰቡ ታውቋል።
የቪኦኤዋ ቪሮኒካ ባልዴራስ ኤግሌሲያስ የላከችው ዘገባ ነው። እንደሚከተለው ተጠናቅሯል።